Wednesday, October 6, 2010

በሰው ወርቅ

ውቢቱዋ ጨረቃ

ጥርት ባለው ሰማይ

አምራና አሸብርቃ

ስትታይ በሙሉ

ከዋክብት ፈዘው

በግርምት ያያሉ፣

እሱዋ ስትሰወር

የሰማዩም አድማስ

ሲዋጥ በጨለማ

ከዋክብት በተራ

ሲቀልቱ እንደሻማ

ከጎን ተደብቃ

ውቢቱዋ ጨረቃ

ትሽቀረቀራለች

ለዳግም ሽብረቃ፡፡